tg-me.com/Mebacha/140
Last Update:
#አትማረኝ 🙏
---------------
#ሚካኤል_እንዳለ
.
ታመው የተነሱ
እግዜርን እረሱ
የሚል ተረት አለ ፥ እሱን ያስታወሰ
ከዕለታት አንድ ቀን ፥ በኔ ላይ ደረሰ
፡፡፡፡
ለ'ለታት ሰባት ቀን ፥ ህመም ተሸክሜ
ከቤቴ ወሳንሳ ለአንድ ሱባ'ዬ የጎን ተጋድሜ
በሞትና በህይወት
በመሄድ በመምጣት
በሁለት አቅጣጫ ፥ ሥጋዬ ሲገፋ
ከቤት ስላልወጣሁ ፥ ሃጢያት 'ካይኔ ጠፋ
፡፡፡፡
ወትሮም በደካሚ
በሌለበት ቋሚ
በዛ ዝለት ጊዜ ፥ ከጓዳው ተኝቶ
እንደ ባህታዊ ፥ በሩን ደጁን ዘግቶ
ከጊዚያዊ ታዛ ፥ ከዚህ ቅዘት ዓለም
እረፍትን ፍለጋ ፥ በዐቱን ለሚያልም
ገዳም እንደመግባት
ለነፍስ እፎይታዋ ፥ ነው ለካ መታመም !!
፡፡፡፡
ታዲያ ምን ያደርጋል
ተኝቼ አልተኛሁኝ
ቀርቼ አልቀረሁኝ
በሳምንቱ እራስጌ ፥ ከህመሜ ዳንኩኝ
ከደጄ እንደወጣው
በመንገድ ላይ ዳሌ ፥ 'ካለም ተዋወኩኝ
፡፡፡፡፡
ለዚህ ለዚህ ነበር
ከቤት ውስጥ መተኛት መታመም ጥቅሙ
እንደ ጥሩ መናኝ በርን አዘግቶ ይለያል 'ካለሙ
እናም ተመስገን ነው በደዌ ሲመቱ ሲታመሙ ማለት
ጉድጓድ እስካልገቡ እድሳት ነውና ህመም ለሰውነት
፡፡፡፡፡
እኔም ይሄን ይዤ
ሥጋዬን በድካም ክፉኛ ሰቅዤ
እንደ ጣናው ፃድቅ እንደ አባ አትማረኝ
በሽታዬ እንዳይድን ፥ ፈጣሪን ለመንኩኝ
ከዝሙት የሚያርቅ ህመም ምንኩስና መሆኑን አወቁኝ
.
#ሚካኤል_እንዳለ
@mebacha
BY መባቻ ©
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/Mebacha/140